ከ 1962 ዓ.ም ጀምሮ ለህሙማን ፈውስ እንሰራለን!
እንኳን ወደ ማይጨው ክሊኒክ በደህና መጡ
ማይጨው ክሊኒክ በ1962 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቀደምት እና ታዋቂ ሐኪሞች ተመስርቶ የተከፈተ የመጀመሪያ የግል ክሊኒክ ነው።
ማይጨው ክሊኒክ
ደረጃውን እና ጥራቱን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት እንሰጣለን
የወንዶች ግርዛት
በማይጨው ክሊኒክ በዘመናዊ መሣሪያዎች የታገዘ፣ ንጽህናው የተጠበቀ እና አስተማማኝ የግርዛት አገልግሎት በባለሙያዎች እንሰጣለን።
About us
እኛ ማን ነን?
ማይጨው ክሊኒክ በ1962 ዓ.ም የተመሰረተ ከኢትዮጵያ ቀደምት የግል ክሊኒኮች መካከል የመጀመሪያው ሲሆን እስከዛሬ ድረስ የህክምና አገልግሎቱን በሰፊው በመስጠት ላይ ይገኛል።
ማይጨው ክሊኒክ በሃገር ውስጥ ተወዳዳሪ በማይገኝለት ዘመናዊ የቀለበት መሳሪያ አስተማማኝ ንጽህና ያለው የግርዛት አገልግሎት ለህጻናት ፣ ለወጣቶች እና ለአዋቂ ወንዶች በመስጠት ላይ ይገኛል።
- የወንዶች ግርዛት አገልግሎት
- ጠቅላላ የሕክምና አገልግሎት
- የላብራቶሪ ምርመራ
ማይጨው ክሊኒክ በአጠቃላይ
1
+
ዓመታት ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት
1
+
ዓመታት ዘመናዊ የወንዶች ግርዛት አገልግሎት
1
+
ደስተኛ ታካሚዎች
ለምን ማይጨው ክሊኒክ?
- ከ1962 ዓ.ም ጀምሮ ጥራት ያለው አገልግሎት
- በታዋቂ ባለሙያዎች የተመሰረተ
- ከ30 ዓመታት በላይ በወንዶች የግርዛት አገልግሎት የታወቅ
ማይጨው ክሊኒክ
ማይጨው ክሊኒክ በኢትዮጵያ የሕክምና ታሪክ ውስጥ የራሱ አሻራ ያለው አንጋፋ ተቋም ሲሆን፤ በ1962 ዓ.ም በሦስት ዝነኛ እና በሀገራችን የሕክምና ዘርፍ ግንባር ቀደም በሆኑ ባለሙያዎች ፕሮፌሰር ጀማል አብዱልቃድር፣ ፕሮፌሰር ደምሴ ሃብቴ እና ዶ/ር አዱኛ መኮንን ተመሰረተ።
በአሁኑ ወቅት በ ዶ/ር ግርማ አዳል ባለቤትነት እና ስራ አስኪያጅነት ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት የታወቀበትን ጥራት ያለው ዘመናዊ የወንዶች የግርዛት አገልግሎት ለህጻናት ፣ ለወጣቶች እና ለአዋቂ ወንዶች በመስጠት በሃገሪቱ ታዋቂነትን አትርፏል።
